ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የ2018 ዓ.ም የሥራ አፈጻጸም ሪፖርትና የ2019 ዓ.ም ዓመታዊ ዕቅድን ገመገመ

ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የ2018 ዓ.ም የሥራ አፈጻጸም ሪፖርትና የ2019 ዓ.ም የበጀት ዓመት የተቋማዊ ዕቅድን በተመለከተ ከዩኒቨርሲቲው ካውንስል አባላትና ከከፍተኛ አመራሮች ጋር የምክክር መድረክ አካሂዷል። መድረኩ የባለፈውን ዓመት የሥራ አፈጻጸም ለመገምገምና የመጪውን ዓመት ተቋማዊ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች በተቀናጀ መልኩ ለመተግበር ያለመ ነው።

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ገብረሚካኤል ወልደገብርኤል በመክፈቻ ንግግራቸው፣ ያለፈውን ዓመት የሥራ አፈጻጸም መገምገምና ለአዲሱ የበጀት ዓመት ዕቅድ ማውጣት የዩኒቨርሲቲውን ስትራቴጂያዊ ግቦች ለማሳካት ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል። የተቋሙን ጥንካሬዎች በማስጠበቅ፣ ያሉ ክፍተቶችን በማረም፣ ግልጽ ዕቅድና ተጠያቂነት በማስፈን እንዲሁም ያሉ ሀብቶችን በብቃት በመጠቀም በትብብር መሥራት እንደሚገባ ጠቁመዋል።

የ2018 ዓ.ም የሥራ አፈጻጸም ሪፖርትና የ2019 ዓ.ም ዓመታዊ ዕቅድ የቀረቡት በስትራቴጂያዊ ጉዳዮች ሥራ አስፈጻሚ አቶ ባህታ አለነ ነው። ተሳታፊዎችም በቀረበው ሪፖርትና ዕቅድ ላይ ጥያቄዎች፣ አስተያየቶችና ምክረ ሐሳቦችን በማቅረብ ሰፊ ውይይት አካሂደዋል።

የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራር በተሳታፊዎች ለተነሱት ጉዳዮች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥቷል። በመጨረሻም የ2019 ዓ.ም ዓመታዊ ዕቅድ ከተሳታፊዎች በቀረቡ ግብዓቶች እንዲጠናከርና በተሳካ ሁኔታ ወደ ትግበራ እንዲገባ የጋራ መግባባት ተደርሷል።

በዓዲግራት ዩኒቨርሲቲን የ2ኛ ዙር የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ተከናወነ

ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲን የበለጠ አረንጓዴና ውብ ለማድረግ ከታቀዱ የክረምት ወቅት መርሃ ግብሮች መካከል አንዱ የሆነው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ዛሬ ነሓሴ 07/2018 ዓ.ም. ለ2ኛ ዙር በዩኒቨርሲቲው ተከናውኗል።

በመርሃ ግብሩ የዩኒቨርሲቲው ፕረዚዳንት ዶ/ር ገ/ምክኤል ወ/ገብርኤል ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች፣ የዩኒቨርስቲው ካውስል አባላት ተሳትፈዋል።

የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ በተቀናጀና በተደራጀ መልኩ በመቀጠል የዩኒቨርሲቲውን ገጽታ በሚያሻሽልና የበለጠ አረንጓዴ በሚያደርግ ሁኔታ እስከ ነሓሴ 15/2018 ዓ.ም. ድረስ የሚቀጥል ይሆናል።

የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ አመራሮች በመጠናቀቅ ላይ የሚገኘውን የሠራተኞች የሕፃናት ማቆያ (Daycare) ማዕከል ጎበኙ

የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ አመራሮች ለመምህራንና ለድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች የሕፃናት ማቆያ (Daycare) አገልግሎት ለመስጠት በዩኒቨርሲቲው ግቢ እየተገነባ ያለውን ማዕከል ጎበኙ።

በጉብኝቱ የዩኒቨርሲቲው ም/ፕሬዚዳንቶች ዶ/ር ገብረኪዳን ተስፋይ እና ፅጋብ አረጋዊ (ተባባሪ ፕሮፌሰር) እንዲሁም ሌሎች የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

የሕፃናት ማቆያ ማዕከሉ ለብዙ የዩኒቨርሲቲው ሠራተኞች የነበረ ጥያቄ በመሆኑ፣ ማዕከሉ በመጠናቀቅ ላይ ያለበትን ደረጃ በማየታቸው አመራሮቹ ደስታቸውን ገልጸዋል።

የዩኒቨርሲቲው የሥርዓተ ፆታና አካቶ ትግበራ ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ይርጋለም ነጋሽ እንደገለጹት፣ የሕፃናት ማቆያ ማዕከሉ በመጠናቀቅ ላይ ሲሆን፣ በቅርቡ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ በመጪው አዲስ ዓመት ለአገልግሎት ክፍት እንደሚሆን ገልጸዋል።

ማዕከሉ በመምህራንና በድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች የሥራና የቤተሰብ ሃላፊነትን ለማመጣጠን እንዲሁም ለሠራተኞች ምቹ የሥራ አካባቢ ለመፍጠር የሚያግዝ አገልግሎት ይሰጣል።

Adigrat University Comprehensive Specialized Hospital has officially launched its Summer Volunteer Health Service Program, bringing essential healthcare services directly to the local community.

As part of the initiative, the hospital’s medical team is providing free blood pressure checks, diabetes screening, HIV testing, and health education sessions to promote preventive healthcare and improve community well-being.

The program also includes a community blood donation drive aimed at strengthening the local blood supply and supporting patients in need.

Community members are encouraged to take advantage of these free health services and actively participate in the program to prioritize their health and contribute to the well-being of the wider community.