አራተኛ ቀን ሀገር አቀፍ የሪሜዲያ ፕሮግራም ፈተና በዓዲግራት ዩኒቨርስቲ በተረጋጋና በተሳካ ሁኔታ እየተከናወነ ይገኛል ።

በዓዲግራት ዩኒቨርስቲ የሀገር አቀፍ የሪሜዲያል ፕሮግራም ፈተና በተፈጥሮ ሳይንስና በማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞችን በተረጋጋ እና በተሳካ ሁኔታ በበይነ መረብ እየተሠጠ አራተኛ ቀን ይዟል። የማሕበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተና በዛሬው ዕለት የሚያልቅ ሲሆን የተፈጥሮ ሳይንስ በነገው ዕለት እንደሚጠናቀቅ የዩኒቨርስቲው የፈተናዎች ማዕከል አስተባባሪ ታደሰ ብርሃነ(ረ/ፕሮፌሰር) ገልፀውልናል።

ሓላፊው በማከል በዚህ ሂደት የላቀ አዎንታዊ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ላሉ ባለድርሻ አካላት በተለይም ለኢትዮቴሌኮም፣ ለከተማው ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ ለዩኒቨርስቲው መረጃና መገናኛ ቴክኖሎጂ ዳይሬክቶሬት፣ ለሰላምና ደህንንት አካላት፣ አመራርና ባለሙያዎች ዩኒቨርስቲው ከልብ የመነጨ ምስጋናና አክብሮት ያቀርባል ሲሉ ተናግረዋል።

በድጋሜ መልካም ዕድል ለውድ ተማሪዎቻችን!!