የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ አመራሮች በመጠናቀቅ ላይ የሚገኘውን የሠራተኞች የሕፃናት ማቆያ (Daycare) ማዕከል ጎበኙ

የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ አመራሮች ለመምህራንና ለድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች የሕፃናት ማቆያ (Daycare) አገልግሎት ለመስጠት በዩኒቨርሲቲው ግቢ እየተገነባ ያለውን ማዕከል ጎበኙ።

በጉብኝቱ የዩኒቨርሲቲው ም/ፕሬዚዳንቶች ዶ/ር ገብረኪዳን ተስፋይ እና ፅጋብ አረጋዊ (ተባባሪ ፕሮፌሰር) እንዲሁም ሌሎች የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

የሕፃናት ማቆያ ማዕከሉ ለብዙ የዩኒቨርሲቲው ሠራተኞች የነበረ ጥያቄ በመሆኑ፣ ማዕከሉ በመጠናቀቅ ላይ ያለበትን ደረጃ በማየታቸው አመራሮቹ ደስታቸውን ገልጸዋል።

የዩኒቨርሲቲው የሥርዓተ ፆታና አካቶ ትግበራ ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ይርጋለም ነጋሽ እንደገለጹት፣ የሕፃናት ማቆያ ማዕከሉ በመጠናቀቅ ላይ ሲሆን፣ በቅርቡ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ በመጪው አዲስ ዓመት ለአገልግሎት ክፍት እንደሚሆን ገልጸዋል።

ማዕከሉ በመምህራንና በድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች የሥራና የቤተሰብ ሃላፊነትን ለማመጣጠን እንዲሁም ለሠራተኞች ምቹ የሥራ አካባቢ ለመፍጠር የሚያግዝ አገልግሎት ይሰጣል።

Adigrat University Comprehensive Specialized Hospital has officially launched its Summer Volunteer Health Service Program, bringing essential healthcare services directly to the local community.

As part of the initiative, the hospital’s medical team is providing free blood pressure checks, diabetes screening, HIV testing, and health education sessions to promote preventive healthcare and improve community well-being.

The program also includes a community blood donation drive aimed at strengthening the local blood supply and supporting patients in need.

Community members are encouraged to take advantage of these free health services and actively participate in the program to prioritize their health and contribute to the well-being of the wider community.