አግኣዚ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በቴክኖሎጂ አጠቃቀም ልምምድ እንዲያገኙ የተዘጋጀው የሞዴል ፈተና በዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ እየተሰጠ ነው።

አግኣዚ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር፣ በ2018 ዓ.ም በኦንላይን የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተማሪዎች አስቀድመው በቴክኖሎጂ አጠቃቀም ልምምድ እንዲያገኙ፣ በ2018 ዓ.ም በትምህርት ቤቱ ደረጃ የተዘጋጀው የሞዴል ፈተና በዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ እየተሰጠ ነው።

Agazi General Secondary School, in collaboration with Adigrat University, is conducting a model examination prepared for the 2018 E.C. academic year. The initiative aims to provide Grade 12 students with practical experience in using technology before sitting for the national examination, which will be administered online in 2018 E.C. The model examination is currently being conducted at Adigrat University to help students become familiar with the online examination system and enhance their readiness.

ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ለሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች በትራፊክ አደጋና በመንገድ ደህንነት ዙሪያ የግንዛቤ ስልጠና መስጠት ጀምራል።

ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ በከተማው ለሚገኙ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች በትራፊክ አደጋና በመንገድ ደህንነት ዙሪያ ያተኮረ የግንዛቤ ስልጠና መስጠት የጀመረ ሲሆን በመጀመርያ ዙር ለፉነተ ብርሃን ተማሪዎች ሰጥቷል። ስልጠናው የተማሪዎችን የመንገድ ደህንነት ግንዛቤ ለማሳደግና የትራፊክ አደጋ መከላከል ባህልን ለማጠናከር ያለመ ነበር።

በስልጠናው ፕሮግራም የዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣ መምህራንና ባለሙያዎች እንዲሁም ከከተማው የህግ አስከባሪ አካላት ተወካዮች ተገኝተዋል።

መድረኩን መ/ር ሃፍቶም ገ/ዮሃንስ ያስተዋወቁ ሲሆን፣ ፕሮግራሙን በይፋ የከፈቱት የዩኒቨርስቲው ማህበረሰብ አገልግሎትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክተር መ/ር ፅጌ አሰፋ ናቸው። በንግግራቸውም የስልጠናውን ዓላማና ጠቀሜታ በማብራራት ተሳታፊዎች በመንገድ ደህንነት ዙሪያ በቂ ግንዛቤ እንዲያገኙ አሳስበዋል።

በዕለቱ መ/ር ተስፋይ ዘርኣይ በመንገድ ደህንነትና በትራፊክ አደጋ ዙሪያ ዝርዝር ገለፃ ያቀረቡ ሲሆን፣ በተለይም የአደጋዎች መንስኤዎችና የመከላከያ መንገዶች ላይ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በመጨረሻም የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር አቶ ገዛኢ ስዩም እንደገለፁት፣ ይህ ዓይነቱ ስልጠና ለተማሪዎች እጅግ ጠቃሚ በመሆኑ ለቀጣይም በተቀናጀ ትብብር መሰል ፕሮግራሞችን ማስቀጠል እንደሚገባ ገልፀዋል።

በተጨማሪም የከተማው መንገድ ደህንነት ተወካይ አቶ ፀሃየ ሓጎስ ተሳታፊዎችን በመቀበል ስለ መንገድ ደህንነት አስፈላጊነት ገለፃ ሰጥተዋል። እንዲሁም ኩማንደር በርሀ ሓድጉ በትራፊክ አደጋዎች ተፅዕኖና በቅድመ ጥንቃቄ አስፈላጊነት ዙሪያ ሰፊ ትንታኔ አቅርበዋል።

Adigrat University Celebrates First Round of English Language Improvement Program (ELIP) Graduates!!

Adigrat, May 17, 2026 – Adigrat University marked a significant milestone as the first round of English Language Improvement Program (ELIP) graduates among its academic staff were honoured in a ceremony held at Debre Damo Hotel. The event brought together ELIP trainees and university officials to celebrate the achievements of the graduating cohort.

The ceremony featured a welcoming speech from Asst. prof. Araya Debalkew, Dean of the College of Social Sciences and Humanities (CSSH), followed by a congratulatory message from Dr. Gebrewahid Tsige, Coordinator of the English Language Improvement Centre (ELIC).

The event concluded with closing remarks from Asst. prof. Girmay Tadele, Director of Academic Programs. The ELIP program is part of Adigrat University’s ongoing efforts to enhance the English language proficiency of its academic staff, supporting quality education and academic excellence.

ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የIntegrated Financial Management Information System (IFMIS) ፕሮጀክት በይፋ ተረከበ።

ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የIntegrated Financial Management Information System (IFMIS) ፕሮጀክትን ከተሳካ የሙከራ ምዕራፍ በኋላ በይፋ የተረከበ ሲሆን፣ በዩኒቨርሲቲው ግቢ በተካሄደ ሥነ-ሥርዓት ይህ ተመልክቷል። በመርሃ ግብሩ ላይ ከገንዘብ ሚኒስቴር፣ ከIBEX/IFMIS ፕሮጀክት ቢሮ፣ ከዩኒቨርሲቲው የሥራ አስፈጻሚዎች እና ከፕሮጀክቱ አስተባባሪዎች የተውጣጡ ተወካዮች ተገኝተዋል።

IFMIS የመንግሥት የፋይናንስ አስተዳደርን ዘመናዊ፣ ዲጂታላዊ፣ ግልጽ እና ቀልጣፋ ለማድረግ የተዘጋጀ ሲስተም ሲሆን፣ በዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የሙከራ ምዕራፉን በተሳካ ሁኔታ አጠናቋል። በዚህ ወቅትም ሲስተሙ የፋይናንስ ሥራዎችን በማቀላጠፍ እና የሀብት አጠቃቀምን በማሻሻል ረገድ ከፍተኛ ውጤት አሳይቷል።

በዝግጅቱ ላይ የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ገብረሚካኤል ወልደገብርኤል ለፕሮጀክቱ ቡድን ምስጋናቸውን ገልጸው፣ ዩኒቨርሲቲው የሲስተሙን ስኬታማ አፈጻጸም በቀጣይነት ለማስጠበቅ ቁርጠኛ መሆኑን ገልጸዋል። የIFMIS ስኬታማ ትግበራም በዩኒቨርሲቲው ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ውስጥ ትልቅ ምዕራፍ መሆኑን አስታውቀዋል።

የአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዚዳንት ተባባሪ ፕሮፌሰር ፅጋብ አረጋዊ በበኩላቸው ሲስተሙን ለማስፈጸም አስተዋጽኦ ላደረጉ ሁሉ ምስጋና አቅርበው፣ IFMIS ዘመናዊና ተጠያቂ የሆነ የፋይናንስ አስተዳደር ሥርዓት ለመገንባት ያለውን ወሳኝ ሚና አጉልተዋል።

ከገንዘብ ሚኒስቴር እና ከIFMIS ፕሮጀክት ቢሮ የተገኙ ተወካዮችም ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ በIFMIS ትግበራ ሂደት ያሳየውን አርአያነት ያለው አፈጻጸም አድንቀው፣ ይህ ተነሳሽነት በሕዝብ ፋይናንስ አስተዳደር ዘርፍ ለቀጣይ ስኬትና ተጨማሪ ፈጠራ ጠንካራ መሠረት እንደሚሆን ገልጸዋል።