በዓዲግራት ዩኒቨርሲቲን የ2ኛ ዙር የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ተከናወነ

ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲን የበለጠ አረንጓዴና ውብ ለማድረግ ከታቀዱ የክረምት ወቅት መርሃ ግብሮች መካከል አንዱ የሆነው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ዛሬ ነሓሴ 07/2018 ዓ.ም. ለ2ኛ ዙር በዩኒቨርሲቲው ተከናውኗል።

በመርሃ ግብሩ የዩኒቨርሲቲው ፕረዚዳንት ዶ/ር ገ/ምክኤል ወ/ገብርኤል ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች፣ የዩኒቨርስቲው ካውስል አባላት ተሳትፈዋል።

የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ በተቀናጀና በተደራጀ መልኩ በመቀጠል የዩኒቨርሲቲውን ገጽታ በሚያሻሽልና የበለጠ አረንጓዴ በሚያደርግ ሁኔታ እስከ ነሓሴ 15/2018 ዓ.ም. ድረስ የሚቀጥል ይሆናል።