የመውጫ ፈተና በሰላምና በተሳካ ሁኔታ ተጠናቀቀ

“ፈተናው ያለምንም የቴክኒክ እና የፀጥታ ችግር በሰላም መጠናቀቁ እንደ ተቋም ትልቅ ኩራት ነው።”

ዶ/ር ገብረሚካኤል ወልደገብርኤል፣ የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት

በሀገር አቀፍ ደረጃ ሲሰጥ የቆየው የመውጫ ፈተና (Exit Exam) በዓዲግራት ዩኒቨርሲቲም በሰላምና በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል። የፈተናውን መጠናቀቅ ተከትሎ የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ገብረሚካኤል ወልደገብርኤል የምስጋና መልዕክት አስተላልፈዋል።

ፕሬዝዳንቱ በመልዕክታቸው ለፈተናው ዝግጅት ከተለያዩ ክፍሎች የተውጣጣ አብይ ግብረ ኃይል ተቋቁሞ ከዝግጅት ሥራ ጀምሮ ፈተናው እስከሚጠናቀቅበት ጊዜ ድረስ ከፍተኛ ርብርብ መደረጉንና ውጤታማ ሥራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።

በተለይም ፈተናው ያለምንም የፀጥታ ችግር እና የቴክኒክ መስተጓጎል በሰላም መጠናቀቁ ለዩኒቨርሲቲው ትልቅ ስኬትና ኩራት መሆኑን አስታውቀዋል።

ፕሬዝዳንቱ በተጨማሪም በፈተናው ሂደት የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ባለድርሻ አካላት ሁሉ ምስጋናቸውን ገልጸዋል። በተለይም ለኢትዮ ቴሌኮም፣ ለከተማው ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ ለዩኒቨርሲቲው የመረጃና መገናኛ ቴክኖሎጂ ዳይሬክቶሬት፣ ለሰላምና ደህንነት አካላት፣ እንዲሁም ለአመራሩና ለመላው ባለሙያ ሠራተኞች ዩኒቨርሲቲው ከልብ የመነጨ ምስጋናና ክብር እንደሚያቀርብ ገልጸዋል።

ከሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሚካሄደው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በቂ ዝግጅት መደረጉን ያስታወቁት ፕሬዝዳንቱ፣ የመውጫ ፈተናውን የወሰዱ ተማሪዎች ጥሩ ውጤት እንዲያስመዘግቡ መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።

እንዲሁም በዓዲግራትና በአካባቢው የሚገኙ በኦንላይን ፈተናቸውን የሚወስዱ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በፈተናው ወቅት የቴክኒክ ችግር እንዳያጋጥማቸው የተለያዩ የልምምድና የዝግጅት ሥራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።

በሌላ በኩል፣ የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የፈተና ማዕከል ኃላፊ ረ/ፕሮፌሰር ታደሰ ብርሃነ እንደገለጹት፣ ዩኒቨርሲቲው በቴክኖሎጂ ዘርፍ ያለውን ከፍተኛ አቅምና ልምድ በመጠቀም በቂ ዝግጅት ማድረጉ፣ እንዲሁም ተማሪዎች የፈተና ሥርዓቱን አክብረው በመፈተናቸው ፈተናው በሰላምና በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን ገልጸዋል።

ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ በሕገ-ወጥ የሰው ዝውውር መከላከል ዙሪያ የግንዛቤና አቅም ማጎልበቻ ስልጠና ሰጠ።

ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ሕግ ትምህርት ቤት በሕገ-ወጥ የሰው ዝውውር መከላከል ዙሪያ ያተኮረ የግንዛቤና አቅም ማጎልበቻ ስልጠና ለተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ሰጥቷል።

በፕሮግራሙ የዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ ከቀያቸው የተፈናቀሉ ወገኖች እና የከተማው ማህበረሰብ ተወካዮች ተሳትፈዋል።

መድረኩን የከፈቱት የማህበረሰብ ተሳትፎና ሽግግር አገልግሎት ዳይሬክተር መምህር ፀጌ አሰፋ ሲሆኑ፣ በንግግራቸው የስልጠናውን ዓላማና አስፈላጊነት በማብራራት ሕገ-ወጥ የሰው ዝውውር በግለሰቦችና በማህበረሰብ ላይ የሚያስከትለውን ከባድ ተፅዕኖ አስገንዝበዋል።

ከሕግ ትምህርት ክፍል መምህር ጎይቶኦም ሙዕዝ በበኩላቸው ስለ ሕገ-ወጥ የሰው ዝውውር ምንነት፣ መንስኤዎች፣ የሕግ ማዕቀፎች እና በሰው ንግድ ዙሪያ የሚፈጸሙ ሕገ-ወጥ ተግባራት ላይ ሰፊ ማብራሪያና ትንታኔ አቅርበዋል።

በተጨማሪም መምህር ስእለይ ሺለሺ ለችግሩ መንስኤ የሚሆኑ ሁኔታዎችና የመከላከያ ስልቶች ዙሪያ ገለፃ ሰጥተዋል። እንደገለጹት ሥራ አጥነት፣ የፖለቲካ አለመረጋጋት እና ተያያዥ ማህበራዊ ችግሮች ሰዎችን ለሕገ-ወጥ የሰው ዝውውር ተጋላጭ ያደርጋሉ። ችግሩን ለመከላከልም ከማህበረሰቡ ጋር በቅንጅትና በትብብር መስራት ወሳኝ መሆኑን አስረድተዋል።

በመጨረሻም ተሳታፊዎች በጉዳዩ ዙሪያ ያላቸውን ሃሳቦች በማካፈል፣ ሕገ-ወጥ የሰው ዝውውርን ለመከላከል ሁሉም አካላት በጋራና በተቀናጀ መንገድ መስራት እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል። በውይይቱም ቀጣይ ሥራዎችን በተጠናከረ ሁኔታ ማስቀጠል እንደሚያስፈልግ ተጠቁሟል።

Final Presentation on the Master Plan and Zoning of Adigrat University Comprehensive Hospital Held.

AT-Con Consulting today delivered the final presentation on the Master Plan and Zoning of the Adigrat University Comprehensive Hospital in the presence of key stakeholders and university officials.

The session was officially opened by Dr. Gebremicael Weldegebriel, President of Adigrat University, who welcomed participants and underscored the importance of clarifying critical aspects of the project before its approval. The Project Manager, Mr. Merhawi, presented the final design revisions, highlighting efforts made to minimize rework and ensure full compliance with the approved Master Plan and Zoning framework

The presentation covered the hospital’s architectural design, electrical, sanitary, and mechanical systems, including modern water supply and waste management facilities. Special attention was given to spatial planning, infrastructure integration, and implementation phases.

Among the participants were Ato Redea Gebreegazabher, Mayor of Adigrat Town, council representatives, and members of the university community. Attendees provided valuable feedback and recommendations aimed at strengthening the project.

The discussions emphasized the importance of collaboration, transparency, and effective implementation to ensure the successful development of a sustainable, modern, and functional healthcare facility that will serve the community and the region.

College of Agriculture and Environmental Sciences Holds Internal Program Review Day to Strengthen Academic Quality.

The College of Agriculture and Environmental Sciences (CAES) at Adigrat University successfully conducted an Internal Program Review Day, bringing together representatives from all departments within the College. The event aimed to critically assess the relevance, quality, and effectiveness of the College’s academic programs and to identify areas for continuous improvement.

Officially opening the event, the Dean of the College, Associate Professor Niguse Gebru, emphasized that program review is one of the College’s core academic quality assurance mechanisms. He noted that the review process helps ensure that curricula, research activities, and community engagement services remain responsive to emerging challenges in agriculture, food security, and environmental sustainability.

“The internal review process enables us to identify gaps, eliminate redundancies, and align our academic programs with national development priorities and industry demands,” the Dean stated.

The review was conducted by a College-level committee comprising representatives from all departments, including Animal Sciences, Plant Sciences, Natural Resource Management, Horticulture, Environmental Sciences, and Agricultural Economics.

During the review session, participants engaged in extensive discussions on several key areas, including:

* Updating and improving course content to reflect current developments in the field;

* Evaluating the balance between theoretical instruction and practical learning experiences, including farm-based training and laboratory work;

* Analyzing graduation rates, student attrition trends, and the effectiveness of academic advising services;

* Assessing the adequacy of laboratory facilities, research farms, and library resources to support teaching, learning, and research activities.

The review provided a valuable platform for reflection, collaboration, and evidence-based decision-making aimed at enhancing academic excellence and ensuring that the College’s programs continue to meet the needs of students, employers, and society at large.