ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና በዛሬው ዕለት ሀገር አቀፍ ፈተና መውሰድ ጀምረዋል። ፈተናው ዛሬ ሰኔ 04/2018 ዓ/ም የተጀመረ ሲሆን ሰኔ 12/2018 ዓ/ም ይጠናቀቃል።
ፈተናው በፌዴራል የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ የሚመራ ሲሆን፣ ለሁሉም ተማሪዎች በኦንላይን ሥርዓት እየተሰጠ ይገኛል። ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲም ሙሉ የአይሲቲ መሠረተ ልማትና የሰው ኃይል ዝግጅት በማድረግ ፈተናውን በተሳካ ሁኔታ እያስፈጸመ ይገኛል።
በአጠቃላይ ዩኒቨርሲቲው በሪሜድያል የነበረ የተሳካ አፈፃፀም በተጠናከረ መንገድ እንዲቀጥል፣ ፈተናው በሰላምና በተሳካ ሁኔታ እንዲካሄድ አስፈላጊ የሆኑ የሰው ኃይል፣ የቴክኖሎጂ እና የሎጂስቲክስ ዝግጅቶችን አጠናቆ ወደ ሥራ ገብቷል።