ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ በሕገ-ወጥ የሰው ዝውውር መከላከል ዙሪያ የግንዛቤና አቅም ማጎልበቻ ስልጠና ሰጠ።

ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ሕግ ትምህርት ቤት በሕገ-ወጥ የሰው ዝውውር መከላከል ዙሪያ ያተኮረ የግንዛቤና አቅም ማጎልበቻ ስልጠና ለተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ሰጥቷል።

በፕሮግራሙ የዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ ከቀያቸው የተፈናቀሉ ወገኖች እና የከተማው ማህበረሰብ ተወካዮች ተሳትፈዋል።

መድረኩን የከፈቱት የማህበረሰብ ተሳትፎና ሽግግር አገልግሎት ዳይሬክተር መምህር ፀጌ አሰፋ ሲሆኑ፣ በንግግራቸው የስልጠናውን ዓላማና አስፈላጊነት በማብራራት ሕገ-ወጥ የሰው ዝውውር በግለሰቦችና በማህበረሰብ ላይ የሚያስከትለውን ከባድ ተፅዕኖ አስገንዝበዋል።

ከሕግ ትምህርት ክፍል መምህር ጎይቶኦም ሙዕዝ በበኩላቸው ስለ ሕገ-ወጥ የሰው ዝውውር ምንነት፣ መንስኤዎች፣ የሕግ ማዕቀፎች እና በሰው ንግድ ዙሪያ የሚፈጸሙ ሕገ-ወጥ ተግባራት ላይ ሰፊ ማብራሪያና ትንታኔ አቅርበዋል።

በተጨማሪም መምህር ስእለይ ሺለሺ ለችግሩ መንስኤ የሚሆኑ ሁኔታዎችና የመከላከያ ስልቶች ዙሪያ ገለፃ ሰጥተዋል። እንደገለጹት ሥራ አጥነት፣ የፖለቲካ አለመረጋጋት እና ተያያዥ ማህበራዊ ችግሮች ሰዎችን ለሕገ-ወጥ የሰው ዝውውር ተጋላጭ ያደርጋሉ። ችግሩን ለመከላከልም ከማህበረሰቡ ጋር በቅንጅትና በትብብር መስራት ወሳኝ መሆኑን አስረድተዋል።

በመጨረሻም ተሳታፊዎች በጉዳዩ ዙሪያ ያላቸውን ሃሳቦች በማካፈል፣ ሕገ-ወጥ የሰው ዝውውርን ለመከላከል ሁሉም አካላት በጋራና በተቀናጀ መንገድ መስራት እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል። በውይይቱም ቀጣይ ሥራዎችን በተጠናከረ ሁኔታ ማስቀጠል እንደሚያስፈልግ ተጠቁሟል።

Final Presentation on the Master Plan and Zoning of Adigrat University Comprehensive Hospital Held.

AT-Con Consulting today delivered the final presentation on the Master Plan and Zoning of the Adigrat University Comprehensive Hospital in the presence of key stakeholders and university officials.

The session was officially opened by Dr. Gebremicael Weldegebriel, President of Adigrat University, who welcomed participants and underscored the importance of clarifying critical aspects of the project before its approval. The Project Manager, Mr. Merhawi, presented the final design revisions, highlighting efforts made to minimize rework and ensure full compliance with the approved Master Plan and Zoning framework

The presentation covered the hospital’s architectural design, electrical, sanitary, and mechanical systems, including modern water supply and waste management facilities. Special attention was given to spatial planning, infrastructure integration, and implementation phases.

Among the participants were Ato Redea Gebreegazabher, Mayor of Adigrat Town, council representatives, and members of the university community. Attendees provided valuable feedback and recommendations aimed at strengthening the project.

The discussions emphasized the importance of collaboration, transparency, and effective implementation to ensure the successful development of a sustainable, modern, and functional healthcare facility that will serve the community and the region.