ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ 220 ላፕቶፕ ኮምፒውተሮችን ከኢትዮ ቴሌኮም ተረከበ።

ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የዲጂታላይዜሽን ሥራዎቹን በተጠናከረ መልኩ ለማስፈጸምና የመምህራንን የቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት ለማሳደግ የሚያገለግሉ 220 ላፕቶፕ ኮምፒውተሮችን ከኢትዮ ቴሌኮም በግዥ ተረክቧል።

የርክክብ ሥነ ሥርዓቱ ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደ ሲሆን፣ በዚህ ወቅት 220 ላፕቶፕ ኮምፒውተሮቹ ለዩኒቨርሲቲው በይፋ ተላልፈዋል።

በርክክቡ ሥነ ሥርዓት ላይ የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ገብረሚካኤል ወልደገብርኤልን እና ምክትል ፕሬዝዳንቶች ተገኝተዋል። ከኢትዮ ቴሌኮም በኩልም የሰሜን ሪጅን ከፍተኛ አመራሮች በሥነ ሥርዓቱ ተሳትፈዋል።

ዩኒቨርሲቲው ይህንን ግዥ በመፈጸም የዲጂታል ትምህርት፣ የመማር ማስተማር ሂደቶችን እና የአካዳሚክ አገልግሎቶችን በቴክኖሎጂ የተደገፈ ለማድረግ እያከናወነው ያለውን ጥረት ይበልጥ እንደሚያጠናክር ተገልጿል።

ዓዲግራት ዩኒቨርስቲ ባለው ዓመት ከኢትዮ ቴሌኮም ለተመሳሳይ አገልግሎት የሚውል 230 ላፕቶፕ ኮምፒውተሮች መግዛቱ የሚታወስ ሲሆን ባጠቃላይ ለመምህራን የሚውሉ 450 ላፕቶፕ ኮምፒውተሮች ተገዝተዋል።

Adigrat University Provides Training on Trauma-Informed Classroom Management and Digital Literacy for Secondary School Teachers.

Adigrat University, through its Department of Teacher Education, organized a capacity-building training program for secondary school teachers and education office officials from Adigrat Town under the theme “Trauma-Informed Classroom Management.” The training aimed to enhance teachers’ psychosocial competencies and strengthen effective classroom management practices in post-crisis learning environments.

The program brought together university leaders, academic staff, officials from the Adigrat Town Education Office, and secondary school teachers from across the town.

Opening the event, Dr. Gebrekidan Tesfay, Vice President for Academic, Research, and Community Engagement, highlighted the long-standing partnership between Adigrat University and local schools. He emphasized the critical role of human capital development in community advancement and underscored the significant contribution teachers make to education, agricultural development, and urban transformation. He further noted the University’s commitment to strengthening technology-supported education and knowledge sharing, stressing the importance of teachers’ psychosocial well-being in creating productive learning environments.

Representing the Adigrat Town Education Office, Mr. Awraneh expressed appreciation for the University’s continued support to local schools and reaffirmed the office’s commitment to further strengthening its collaboration with the University.

As part of the training, Dr. Teklebrhan Gebremeskel delivered a comprehensive session on trauma, the psychological impacts of war and other crises, and modern pedagogical approaches for supporting learners affected by adversity. Particular emphasis was given to effective classroom management strategies and trauma-sensitive teaching practices.

In a separate session, Mr. Gebrekristos Gebru from the Department of Computer Science presented on “Digital Literacy Essentials, Information Sharing, and Communication Technologies,” providing participants with practical insights into digital tools and technology-enhanced teaching and learning.

The training equipped participants with valuable knowledge and skills in both psychosocial support and digital literacy. The program concluded with an interactive discussion and question-and-answer session, during which participants called for the continuation and expansion of similar capacity-building initiatives in the future.

የመውጫ ፈተና በሰላምና በተሳካ ሁኔታ ተጠናቀቀ

“ፈተናው ያለምንም የቴክኒክ እና የፀጥታ ችግር በሰላም መጠናቀቁ እንደ ተቋም ትልቅ ኩራት ነው።”

ዶ/ር ገብረሚካኤል ወልደገብርኤል፣ የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት

በሀገር አቀፍ ደረጃ ሲሰጥ የቆየው የመውጫ ፈተና (Exit Exam) በዓዲግራት ዩኒቨርሲቲም በሰላምና በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል። የፈተናውን መጠናቀቅ ተከትሎ የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ገብረሚካኤል ወልደገብርኤል የምስጋና መልዕክት አስተላልፈዋል።

ፕሬዝዳንቱ በመልዕክታቸው ለፈተናው ዝግጅት ከተለያዩ ክፍሎች የተውጣጣ አብይ ግብረ ኃይል ተቋቁሞ ከዝግጅት ሥራ ጀምሮ ፈተናው እስከሚጠናቀቅበት ጊዜ ድረስ ከፍተኛ ርብርብ መደረጉንና ውጤታማ ሥራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።

በተለይም ፈተናው ያለምንም የፀጥታ ችግር እና የቴክኒክ መስተጓጎል በሰላም መጠናቀቁ ለዩኒቨርሲቲው ትልቅ ስኬትና ኩራት መሆኑን አስታውቀዋል።

ፕሬዝዳንቱ በተጨማሪም በፈተናው ሂደት የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ባለድርሻ አካላት ሁሉ ምስጋናቸውን ገልጸዋል። በተለይም ለኢትዮ ቴሌኮም፣ ለከተማው ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ ለዩኒቨርሲቲው የመረጃና መገናኛ ቴክኖሎጂ ዳይሬክቶሬት፣ ለሰላምና ደህንነት አካላት፣ እንዲሁም ለአመራሩና ለመላው ባለሙያ ሠራተኞች ዩኒቨርሲቲው ከልብ የመነጨ ምስጋናና ክብር እንደሚያቀርብ ገልጸዋል።

ከሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሚካሄደው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በቂ ዝግጅት መደረጉን ያስታወቁት ፕሬዝዳንቱ፣ የመውጫ ፈተናውን የወሰዱ ተማሪዎች ጥሩ ውጤት እንዲያስመዘግቡ መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።

እንዲሁም በዓዲግራትና በአካባቢው የሚገኙ በኦንላይን ፈተናቸውን የሚወስዱ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በፈተናው ወቅት የቴክኒክ ችግር እንዳያጋጥማቸው የተለያዩ የልምምድና የዝግጅት ሥራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።

በሌላ በኩል፣ የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የፈተና ማዕከል ኃላፊ ረ/ፕሮፌሰር ታደሰ ብርሃነ እንደገለጹት፣ ዩኒቨርሲቲው በቴክኖሎጂ ዘርፍ ያለውን ከፍተኛ አቅምና ልምድ በመጠቀም በቂ ዝግጅት ማድረጉ፣ እንዲሁም ተማሪዎች የፈተና ሥርዓቱን አክብረው በመፈተናቸው ፈተናው በሰላምና በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን ገልጸዋል።