Adigrat University School of Law Conducts Internal Program Review.

The School of Law at Adigrat University successfully conducted its Internal Program Review as part of its ongoing commitment to academic quality and continuous improvement.

During the review, the School’s Review Committee presented its findings and recommendations, focusing on curriculum relevance, alignment with national and regional justice system priorities, teaching and learning practices, and compliance with academic and professional standards.

Participants actively engaged in the discussion and provided valuable feedback and constructive suggestions to further strengthen the program.

The workshop concluded with a reaffirmation of the School’s commitment to enhancing the quality of legal education and developing a more responsive and practice-oriented law program.

ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ በ“የተገልጋይ እርካታ” ዙሪያ ሥልጠና ሰጠ።

ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ በዛሬው ዕለት “የተገልጋይ እርካታ” በሚል ርዕስ ያተኮረ ሥልጠና አካሂዷል። ሥልጠናው የአገልግሎት ጥራትን ለማሻሻልና የተገልጋዮችን እርካታ ለማሳደግ ያለመ ሲሆን፣ በዩኒቨርሲቲው እና ከውጭ ተቋማት የተውጣጡ ተሳታፊዎችን አሳትፏል።

በፕሮግራሙ የዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣ ከጥቃቅንና አነስተኛ ማኅበራት የተውጣጡ ተወካዮች፣ ከሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ መምህራን እንዲሁም የተለያዩ የዩኒቨርሲቲው ሠራተኞች ተሳትፈዋል።

የዕለቱን መርሃ ግብር መምህር ወንድሙ ሐለፎም በማስተዋወቅ ተሳታፊዎችን እንኳን ደህና መጣችሁ ብለው ተቀብለዋል። በመክፈቻ ንግግራቸው የዩኒቨርሲቲው የማኅበረሰብ አገልግሎትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክተር ረ/ፕሮፌሰር ፅጌ አሰፋ የሥልጠናውን ዓላማ፣ አስፈላጊነት እና በአገልግሎት ማሻሻያ ሂደት ያለውን ሚና በተመለከተ ገለጻ አድርገዋል።

በመቀጠል የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ ዲን ረ/ፕሮፌሰር መሰረት መረሳ ስለ “የተገልጋይ እርካታ” ጽንሰ-ሐሳብ፣ አስፈላጊነትና ተቋማዊ ጠቀሜታ አጠቃላይ ግንዛቤና ትንተና አቅርበዋል።

በመቀጠልም ከቱሪዝም ትምህርት ክፍል መምህር አብርሃ ገብረመስቀል እና ከሎጂስቲክስና ሰፕላይ ቼይን ማኔጅመንት ትምህርት ክፍል መምህር ግርማይ ተስፋይ በጉዳዩ ላይ ሰፊ ማብራሪያና ተግባራዊ ሥልጠና ሰጥተዋል። በሥልጠናውም የተገልጋይ እርካታ ምንነት፣ የአተገባበር ስልቶች፣ ተቋማዊ ጥቅሞች እና በአገልግሎት ጥራት ላይ የሚያሳድረው ተጽዕኖ በዝርዝር ተዳስሷል።

በመጨረሻም ተሳታፊዎች ሥልጠናው ጠቃሚና ወቅታዊ መሆኑን ገልጸው፣ ከቀረቡት ጽንሰ-ሐሳቦችና ተግባራዊ ልምዶች ብዙ እንደተጠቀሙ አስረድተዋል። በተጨማሪም መሰል የአቅም ግንባታ ሥልጠናዎች ወደፊትም በቀጣይነት ተጠናክረው እንዲሰጡ ጥያቄና አስተያየታቸውን አቅርበዋል።

በመጨረሻም ለሥልጠናው ተሳታፊዎች የተሳትፎ ሰርቲፊኬት የተበረከተ ሲሆን፣ ፕሮግራሙም በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።

የኢንጅነሪንግና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ የትምህርት ፕሮግራሞች ግምገማ ሪፖርት አቀረበ።

በዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የኢንጅነሪንግና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ ሥር በሚገኙ 10 የመጀመሪያ ዲግሪ (BSc) ፕሮግራሞች ላይ ለአራት ወራት ሲካሄድ የቆየው የትምህርት ፕሮግራም ግምገማ (Academic Program Review) ሪፖርት በዛሬው ዕለት ቀርቧል።

የዕለቱን ፕሮግራም ዶ/ር ሱዑድ ያስተዋወቁ ሲሆን፣ የመክፈቻ ንግግሩን ያደረጉት የኮሌጁ ዲን ረ/ፕሮፌሰር እሱባለው አወቀ ነበሩ።ኮሌጅ ዲኑ በንግግራቸው የፕሮግራም ግምገማ ሥራው በትምህርት ሚኒስቴር በተሰጠው መመሪያ መሠረት ለአራት ወራት በትጋት ሲከናወን መቆየቱን ገልጸው፣ ሪፖርቱ ወደ ግምገማ መድረክ በመድረሱ የሂደቱ አንዱ ወሳኝ ምዕራፍ መጠናቀቁን አስታውቀዋል። በቀጣይም ሁሉም አካላት በትብብር በመሥራት የማሻሻያ ሂደቱን እንደሚያስቀጥሉ ገልጸዋል።

በመቀጠል የአካዳሚክ ፕሮግራሞች ዳይሬክተር ረ/ ፕሮፌሰር ግርማይ ታደለ እንደገለጹት፣ የፕሮግራም ግምገማ ሂደቱ ሰፊ ጊዜና ጥረት የሚጠይቅ ሥራ መሆኑን ጠቁመዋል። እንዲሁም በትምህርት ሚኒስቴር በተቀመጠው መስፈርት መሠረት የሚከናወነው ይህ ግምገማ ፕሮግራሞችን ለመዝጋት ወይም ለመቀነስ ሳይሆን በማሻሻያ ሂደት በኩል የትምህርት ጥራትን ለማሳደግና ማኅበረሰቡን በተሻለ ሁኔታ ለማገልገል ያለመ መሆኑን ገልጸዋል።

ከዚያም ከእያንዳንዱ የትምህርት ክፍል የተወከሉ የኮሌጁ የፕሮግራም ክለሳ ኮሚቴ ኣባላት በየፕሮግራሞቻቸው የተከናወኑ የፕሮግራም ክለሳ ሥራዎችንና ውጤቶቻቸውን በዝርዝር አቅርበዋል።

በመድረኩ የተሳተፉ አካላት ባቀረቡት ሪፖርቶች ላይ ገንቢ አስተያየቶችና ድጋፍ ሰጪ ሃሳቦችን ያቀረቡ ሲሆን፣ የተነሱ ጥያቄዎችና ማብራሪያ የሚሹ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።በመጨረሻም ከመድረኩ በተሰጡ ምላሾችና ማብራሪያዎች ፕሮግራሙ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።

ይህ የፕሮግራም ግምገማ ሂደት በኮሌጁ የሚሰጡ የትምህርት ፕሮግራሞችን ጥራት፣ ተዛማጅነትና ውጤታማነት ለማጠናከር የሚያግዝ አስፈላጊ እርምጃ መሆኑ ተጠቁሟል።

የ12ኛ ክፍል ፈተና ተፈታኞች በዓዲግራት ዩኒቨርስቲ ልምምድ እየሰሩ ይገኛል።

በዓዲግራት ከተማ የሚገኙ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ከሰኔ 23/2018 ዓ/ም ጀምሮ ለሚካሄደው የ12ኛ ክፍል ፈተና የቴክኒክ ችግር እንዳይገጥማቸው ትምህርት ቤቶቹ ለዩኒቨርስቲው ባቀረቡት ጥያቄ መሰረት በዩኒቨርስቲው ድጋፍ እየተደረገላቸው ይገኛል።

ዓዲግራት ዩኒቨርስቲ በትምህርት ዘርፍ የሚደረግ ድጋፍ ለሃገርና ቤተሰብ ጠቃሚ የሚሆን ትውልድ ለማፍራት ትልቅ ሚና እንዳለው በማመን እስካሁን በአከባቢው የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ሰፋፊ ድጋፍ ስያደርግ ቆይቷል።

ሰኔ 23/2018 ዓ/ም ጀምሮ ለሚሰጥ ሃገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና በዓዲግራት እና ኣከባቢው የሚገኙ በበይነ መረብ ፈተናቸው የሚወስዱ ተማሪዎች በፈተናው ወቅት የቴክኒክ ችግር እንዳይገጥማቸው የልምምድ ስራዎች በተከታታይ ቀናት እየሰሩ እንደሆነና የዩኒቨርስቲው የኣይሲቲ ባለሙያዎች ድጋፍ እያደረጉላቸው እንደሆነ የዓዲግራት ዩኒቨርስቲ ኣይሲቲ ዳይሬክተሩ ነጋሲ ታደሰ ገልፀውልናል።